ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሆረ ፊንፊኔ ባህላዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት ተከብሮ መጠናቀቁን ገልጸዋል::
የሆረ ፊንፊኔ በዓል በስኬት መጠናቀቅ የአባገዳዎችና ሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም የከተማችን ነዋሪዎች ላበረከቱት አስተዋጽዖ ከንቲባ አዳነች አመስግነዋል::
በተጨማሪ በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎች እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቀን እና ምሽት በቂ አቅርቦት እና አገልግሎት ለእንግዶቹ በመስጠት ለበአሉ በድምቀት መጠናቀቅ ትልቅ ድርሻ የተጫወቱ መሆኑን የገለጹት ከንቲባ አዳነች በ5ቱም በር ያለው የከተማችን ነዋሪ የወንድማማች እና እህትማማች መንፈስን ተላብሶ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት እንግዶቹን በፍቅር መቀበሉን ጨምረው ገልጸዋል::
ከንቲባ አዳነችች አቤቤ በዓሉ በድምቀቅ እንዲጠናቀቅ አስተዋፅዖ ያበረከቱ የከተማችን ነዋሪዎችን፣ ወጣቶችን፣ የጸጥታ አካላትን እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የከተማ አስተዳደሩን አመራሮች አመስግነዋል::
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.