
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤው ለ2017 ዓ.ም ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን በማፅደቅ ተጠናቅቋል::
በዚህም መሰረት:-
1. ወ/ሮ ቆንጆት ደበላ - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ሕጻናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ(በሽግሽግ)
2. አቶ አወሌህ መሐመድ ኦመር - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
3. ወ/ሮ አይሻ መሐመድ አደን - የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር
4. ኢ/ር ሕይወት ሣሙኤል ጸጋዬ - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር
5. ሲ/ር ሶፊያ አለሙ - የሴቶች፣ የወጣቶችና ህፃናት ቋሚ ኮሚቴ ሆነው ተሹመዋል::
በሌላ በኩል ተጨማሪ በጀቱ በከተማዋ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ልማቶችን ለማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑንም ምክር ቤቱ ተወያይቶ በሙሉ ድፅ አፅድቋል፡፡
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.