ለሚሰጡት አገልግሎት ጉቦ የጠየቁ አመራሮች በቁ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ለሚሰጡት አገልግሎት ጉቦ የጠየቁ አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የቄራዎች ድርጅት የሚሰጠውን አገልግሎት ለማግኘት የሄዱ ተገልጋዮችን ገንዘብ የጠየቁ ሁለት ተጠርጣሪ አመራሮች ፣ 1ኛ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር   አቶ ሰይድ  እንድሪስ  ከማል  እና 2ኛ ምክትላቸው አቶ ዮሴፍ ድሪብሳ ማሞ ገንዘብ ካላመጣችሁ አገልግሎት አታገኙም  በማለት ፤ እንግልት ሲፈጠሩ ቆይተው  በደረሰ ጥቆማ በዛሬው ዕለት ከተገልጋይ ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘው በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡  

ተገልጋዬች ተከታትለዉ ለሰጡት ጥቆማ እያመሰገንን ፣ በቀጣይም ሙስናን ለመከላከል በሚደረገው ትግል ከጎናችን በመሆን መተባበራችሁን እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርብለን።

በቀጣይም ህብረተሰቡ እንደዚህ አይነት የሙስና ተግባራትን ሲመለከት ለ ከንቲባ ጽ/ቤት  የሙስና ወንጀል ጥቆማ ተቀባይ በመጠቆም  ሙስናን የመከላከል ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ እናሳስባለን።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.