በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በዘላቂነት በኮሪደር ልማት ደረጃ እንደሚሰሩ፡- ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም አካባቢዎች የኮሪደር ልማት ስራን ለማዳረስ ምን እንደታቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ በቂ ዝግጅትን የሚጠይቅ ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም በዚህ ዓመት አዲስ የኮሪደር ልማት ስራዎች እንደማይኖር የገለጹት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ነገር ግን በመዲናዋ የሚሰሩ አዳዲስ የመንገድ መሠረተ ልማት ስራዎች በኮሪደር ልማት እስታንዳርድ ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተደርጎ ይሰራሉ ብለዋል፡፡
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.