ባለስልጣኑ በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት የ300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ ።
ድርጅቱ ፍሳሽ ቆሻሻን ባልተገባ መንገድ ወደ ወንዝ ሲለቅ በመገኘቱ ቅጣቱ ተላልፎበታል ።
ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት ጠንካራ ክትትል በማድረግ
አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ተቋማትና ግለሰቦች ማንኛውም አይነት ቆሻሻ ወደ ወንዝና የወንዞች ዳርቻ ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማትን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.