ዛሬ ያስመረቅነው ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የሲኒማ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ዛሬ ያስመረቅነው ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የሲኒማ ማዕከል በአይነቱ ልዩና ለኪነጥበብ እድገት አዲስ ምዕራፍ ከፋች መሆኑን ሳበስር በደስታ ነው !

መንግስት የኪነጥበብን ወሳኝ ሚና በመረዳትና ልዩ ትኩረት በመስጠት በቢሊዮኖች በጀት መድቦ በአይነታቸው ልዩና ዘመናዊ ለሲኒማ ፣ለቲያትር ራሳቸውን የቻሉ ትልልቅ ማዕከላት ሲገነባ ፤ በኪነጥበብ ዘርፈ የተሰማራችሁ ከያኒያንና የጥበብ ቤተሰቦች ሁሉ፣ ለአገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሰረት የሚሆኑ የጥበብ ስራዎችን በማበርከት፣ ታሪክ የማይዘነጋው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንደምታበረክቱ  በማመን ነው ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.