የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሩብ ዓመቱ በባ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሩብ ዓመቱ በባህል እና ኪነ-ጥበብ ካከናወናቸው ተግባር ውስጥ:-

👉ቋሚ፣ተንቀሳቃሽና የማይዳሰሱ ቅርሶችን 400 ለመመዝገብ ታቅዶ በደረጃው ባላው አደረጃጀትና ባለድርሻ በመጠቀም ሙሉ ለሙሉ መፈጸም ተችሏል፡፡ 

👉 ለ406 ቋሚ፣ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ጥበቃና እንክብካቤ ማድረግ ተችሏል::

👉 3 ሕዝባዊና መንግስታዊ ብሔራዊ የበዓል ቀናትና ኩነቶችን በማክበርና ክዋኔውን በማስተዋወቅ ታቅዶ የቡሄ ፣መስቀል እና  የኢሬቻ  ሶስቱም በዓላት በሲንፖዚየም እና በኤግዝብሽን ለማክበር ተችሏል፡፡ 

👉 ለ 316,311 ተገልጋዮች የንባብ አገልግሎት መስጠት ተችሏል::

👉  116 የተለያዩ የኪነ-ጥበብ ስራዎች ተዘጋጅተዉ ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ አቅዱን ሙሉ በሙሉ ማሳካት ተችሏል፡፡ 

👉ለ 62 ተቋማት የሙያ ብቃት አገልግሎት መስጠት ተችሏል።  

👉  68 አማተር የኪነ-ጥበብ ክበባትን ለማቋቋም ታቅዶ በተለያዩ ክ/ከተሞች 17  ክበባትን ማቋቋም ተችሏል::

👉 በጠቃሚ ባህላዊ እሴቶችና ሀገር በቀል ዕውቀቶች ፋይዳና ልማት ዙሪያ የውይይት መድረኮችንን ለማዘጋጀት ታቅዶ “የተረጅነት አስተሳሰብ” እና 7ተኛውን የኢሬቻ ፎረም “ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት’’ በሚል መነሻ  ሀሳብ ሁለት ግዜ ውይይት ማከናወን ተችሏል::


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.