ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስናካሄድ የነበረዉ የስ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስናካሄድ የነበረዉ የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረካችን ተጠናቅቋል ።

በግምገማ መድረኩ ማጠቃለያ በሩብ ዓመቱ እና በ90 ቀናት ስራዎቻችን በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የትኩረት መስኮች  የተገኙ  በርካታ አበረታች ዉጤቶችን ይበልጡን አጠናክሮ ለማስቀጠል ፣ የታዩ ጉድለቶችን ፣ ብልሹ አሰራሮችን በፍጥነት ለማረም  እና ዉጤታማነትን በወጥነት አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጠናል  ።

በበጀት አመቱ ቀሪ ጊዜያት ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባሮቻችን ተጠናክረዉ የሚቀጥሉ ይሆናል ፣ በዚህም የኑሮ ጫናን ለመቀነስ  የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርት አቅርቦት መሻሻሎችን ማስቀጠል ፣ የከተማዉን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ፣ የገቢ አሰባሰባችንን ማሳደግ ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር የታየዉን  ተስፋ ሰጪ ለዉጥ ይበልጡን ማስፋት፣ የስራ ዕድል ፈጠራን በማሳደግ የህዝባችንን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት  ይበልጡን አጠናክረን የምናስቀጥል ይሆናል ።

ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 
 
 ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
  https://linktr.ee/addisababacommunication


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.