ዛሬ በከተማችን በ 2ኛዉ ምዕራፍ ተጀምረዉ በተጠ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ዛሬ በከተማችን በ 2ኛዉ ምዕራፍ ተጀምረዉ በተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ከፍተኛ አስተዋፆ ያደረጉ አካላትን አመስግነናል:: ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ዛሬ በከተማችን በ 2ኛዉ ምዕራፍ ተጀምረዉ በተጠናቀቁ  የኮሪደር ልማት  ስራዎች ላይ ለ አራቱ ማለትም (1) ከመስቀል አደባባይ መገናኛ - ሳዉዝ ጌት፣ (2) ከአንበሳ ጋራዥ -ጎሮ ፣  (3) ከአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ፣ ጎሮ ፣ቦሌ ቪ አይ ፒ ተርሚናል እንዲሁም ከሳር ቤት -ጀርመን አደባባይ ፣ጋርመንት ፉሪ አደባባይ ኮሪደር ልማት ስራዎች ላይ ከፍተኛ አስተዋፆ ያደረጉ አካላትን  አመስግነናል ።

በዚህም በከፍተኛ የስራ ተነሳሽነት ሌት እና ቀን ሲሰሩ ለነበሩ  ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች እና ሰራተኞች ፣ ኮንትራክተሮች ፣ አማካሪዎች ፣ማህበራት ፣በጎ ፈቃደኞች እና ሌሎችም  ለነበራቸዉ ከፍተኛ አስተዋፆ እና ትዉልድ ተሻጋሪ ስራ አመስግነናል ።

በተለይም መላዉ የከተማችን  ነዋሪዎች ለሚነዙ ሀሰተኛ አሉባልታዎች  ጆሮ ሳይሰጥ   የልማት ተነሺ የሆኑትም ያልሆኑትም  ለጋራ ልማት በመተባበር  ፣ ቡና እያፈላ ፣ ዉሃ እያቀረበ ለልማት ስራዉ ዉጤታማነት ላሳየዉ ከፍተኛ ድጋፍ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለዉ ።

በ 1ኛ እና በ2ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ስራዎች ከተጠናቀቁ መሰረተ ልማቶች መካከል 342 ኪ.ሜ የእግረኛ መንገድ ፣  185 ኪ.ሜ  የተሽከርካሪ መንገድ ፣241 ኪ.ሜ የሳይክል መንገድ ፣ ዘመናዊ የመንገድ መብራቶች ፣ በርካታ የህዝብ መገልገያ እና መዝናኛ ቦታዎች ፣ በርካታ የሕዝብ አገልግሎት መስጫ መሰረተ ልማቶች ፣ 101 የህፃናት መጫወቻዎች ፣ 155 የስፓርት ማዘዉተሪያዎች ፣ 153 ዘመናዊ ፓርኪንግ እና ተርሚናሎች እንዲሁም 210 የሕዝብ መፀዳጃዎች ተገንብተዉ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ፣

ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዞቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.