ዓለም አቀፍ የጸረ ጾታዊ ጥቃት ቀን በዓለም ለ34ኛ ጊዜ ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ይከበራል።
ዓለም አቀፍ የጸረ ጾታዊ ጥቃት ቀን ወይም ነጭ ሪቫን ቀን "ጥቃትን የማይታገስ ማኅበረሰብ ለትውልድ ግንባታ" በሚል መሪ መልዕክት የሚከበረው የጸረ ጾታዊ (የነጭ ሪቫን) ቀንም በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ የኀይል ጥቃት እና የሰብዓዊ መብት ጥሰትን መከላከል ዋና ዓላማው ያደረገ ነው።
የጸረ ጾታዊ ቀን የሚከበርበት ምክንያት ሥርዓተ ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን በዘላቂነት ለመከላከል እና ለዓላማው መሳካት የወንዶችን አጋርነት ለማጠናከር ነው።
የሴቶች ጥቃትን የሚጸየፍ ማኅበረሰብ እስኪፈጠር የጸረ ጾታዊ ጥቃት መከላከል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ።
ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች በሴቶች እና ሕጻናት ላይ የሚያስከትሉት ችግር ዘርፈ ብዙ በመኾኑ ይህን ለመከላከል ባለፉት ጊዜያት ውጤታማ ሥራዎች ተሠርተዋል፤ የዘንድሮውን የንቅናቄ ሥራም ውጤታማ ለማድረግ ይሠራል ።
ጾታዊ ጥቃቶች ለአካላዊ እና አዕምሮዓዊ የጤና፣ የሥነ ልቦናዊ እና የማኅበራዊ ችግሮችን እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊ ጥገኝነት ያጋልጣል።
ድርጊቱን ለማስቆም የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እና ሕጋዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥም ከመቼውም ጊዜ በላይ ይገባል።
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.