የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ ትኩረት የተደረገባቸዉ ስራዎች እና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችን በዝርዝር ቀርቧል::
ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገቡ ስኬቶች በጋራ የተደረጉ ጥረቶች እና የነዋሪዎቻችን ንቁ ተሳትፎ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል::
👉የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መፍታት
👉የትራንስፖርት አቅርቦት ማነቆዎችን ማስወገድ
👉የውሀ አቅርቦት እና የቤት ልማት ስራዎችን ማፋጠን
👉የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል
👉የተጀመረውን የመሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ማእከላትን ማስፋት
👉በተቋማት መካከል ያለውን የአፈፃፀም ልዩነት ማቀራረብ
👉ለህዝብ አገልግሎት የለሙ ቦታዎችን ለታለመላቸው አላማ ብቻ እንዲውሉ ማስቻል
👉የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቁርጠኝነት ለመፍታትና የነዋሪዎቻችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቀጣይ ትኩረት የምንሰጥባቸው ጉዳዮች መሆናቸዉን የአዲስ አባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር አባላት አሳስበዋል፡፡
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.