በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተግባራዊ እየተደ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" አካል የሆነው "አዲስ አበባ ታምርት" ንቅናቄ በከተማዋ ኢኮኖሚ ላይ አዲስ ተስፋና ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።

ከሸማችነት ወደ አምራችነት - በ"አዲስ አበባ ታምርት"  

- ንቅናቄው የከተማዋን የኢኮኖሚ መዋቅር በመቀየር ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ ነው። 

- ከዚህ በፊት በግብዓትና በኤሌክትሪክ እጥረት ከአቅም በታች ያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች፣ አሁን ላይ የማምረት አቅማቸውን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድገዋል። 

- በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ "የኢትዮጵያን ምርት ይግዙ" የሚለው ጥሪ ዛሬ በተጨባጭ ውጤት ታጅቦ በምግብና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅና በኮንስትራክሽን ዘርፎች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ጥራት ባላቸው ምርቶች መተካት ተችሏል። 

- ንቅናቄው በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶችና ሴቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ፣ የቴክኖሎጂና የክሕሎት ሽግግር እንዲመጣ አድርጓል። 

- በርካታ አነስተኛ አምራቾች ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪነት ተሸጋግረዋል፤ ጠንካራ የገበያ ትስስርም ተፈጥሮላቸዋል። 

- ከጫማ እስከ አልባሳት፣ ከቤት ዕቃዎች እስከታሸጉ ምግቦች ድረስ አዲስ አበባ ከውጭ የምታስገባቸውን ምርቶች በሀገር ውስጥ መተካት አስችሏታል። 

- የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ ስኬት ቁልፍ የሆኑ ድጋፎችን እያከናወነ ይገኛል።

- በከተማዋ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ ሼዶች ለወጣቶችና ለባለሀብቶች ተላልፈው፣ አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል እያደረጓት ይገኛሉ።

- ዘመናዊ የኢንዱስትሪ መንደሮችን በማስፋፋት ለአምራቾች ምቹ የሥራ ቦታ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። 

- ለኢንተርፕራይዞች የማሽነሪ ግዢ የሚውል የሊዝ ፋይናንስና የብድር አገልግሎት እንዲመቻችና የቢሮክራሲ ማነቆዎችን የሚፈታ "የአንድ ማዕከል" አገልግሎት እንዲቋቋም ተደርጓል። 

- የባንክ በሮች ለአምራቾች ክፍት ሆነዋል። ንቅናቄው አምራቾች በቀላሉ የሥራ ማስኬጃ ብድር የሚያገኙበትን መንገድ ከማመቻቸቱም በላይ፣ በቀጥታ ከሸማቹ ጋር የሚገናኙባቸውን ታላላቅ ባዛሮች በማዘጋጀት የገበያ ሰንሰለቱን አሳጥሮታል። 

- በተጨማሪም  አምራቾች ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ትላልቅ ባዛሮችንና ኤግዚቢሽኖችን በማዘጋጀት በኩልም ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረገ ይገኛል።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.