ድጋፍ–ለዓቅመ-ደካሞች እና ድጋፍ ለሚሹ ሁሉ!
በአዲስ አበባ፥ በበዓላት ዋዜማ ለዓቅመ-ደካሞች እና ድጋፍ-ለሚሹ ሁሉ የሚደረገው ድጋፍ፣ የከተማዋን የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል በተግባር የሚያሳይ ትልቅ ማህበራዊ እሴት ነው።
ከተማ አስተዳደሩ፣ ከግብረ-ሰናይ ድርጅቶችና ባለሀብቶች በመቀናጀት፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች፣ አረጋውያንና ወላጅ አልባ ሕፃናት መሰረታዊ የሆኑ የበዓል መዋያ ምርቶችን በነጻ ያጋራል ወይም በታላቅ ቅናሽ ያቀርባሉ።
ይኽም፥ በኢኮኖሚ አቅም ማነስ ምክንያት፣ በዓሉን ማክበር ለሚከብዳቸው ወገኖች ትልቅ ተስፋና እፎይታን እየፈጠረ ሲሆን፤ ድጋፉ በዓሉን በደስታ እና ሳይጎድልባቸው እንዲያከብሩ እያደረገ የሚገኝ፤ የበጎነት ውብ ገፅታዋ እየኾነ ነው ፡፡
“50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ፤ ለ50 ሰው ጌጥ”ነውና አባባሉ፣ በከተማችን አዲስ አበባ መደጋገፍ፣ መተባበር እና መተጋገዝ፥ ድጋፍ ለሚሹ ዓቅመ-ደካሞች ተስፋ፣ የበዓል ፌሽታ መኾን ከጀመረ ሰነባብቷል፡፡
“በጎነት አያጎድልም”!
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.