ምርትን ከአምራቹ፥ ለሸማቹ፤ ከገበሬው ለነዋሪው!
በውቢቷ ከተማ አዲስ አበባ፣ በአምስቱም መግቢያ በሮች የሚገኙ የገበያ ማዕከላት፣ ለከተማዋ የኢኮኖሚ ዋስትና ከመሆናቸው በላይ ለሸማቹ ሕበረተሰብ እየሰጡ ያሉትን እፎይታ የጎላ ነው፡፡
እነዚህ ማዕከላት፣ ከየአቅጣጫው ከሚመጡ አምራቾች ጋር ቀጥተኛ ትስስር በመፍጠር፣ የግብርና ምርቶችና የእንሰሳት ተዋጽኦዎችን ሳይዘገዩና ትኩስነታቸውን ሳይቀንሱ፣ ወደ ከተማዋ እንዲገቡ በማድረግ ነዋሪው ኪሱ ሳይጎዳ ጤናውን እንዲጠብቅ አስችለዋል፡፡
በተለይም፣ በከተማዋ መሀል የሚፈጠረውን የምርት እጥረት ከመቅረፍ በተጨማሪ፣ በጅምላና በችርቻሮ ንግድ መካከል ያለውን የደላላ ሰንሰለት በማሳጠር ብሎም በመቁረጥ ለነዋሪው በተመጣጣኝ ዋጋ ምርት እንዲቀርብ በማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡
በአምስቱም አቅጣጫዎች የሚገኙት እነዚህ የንግድ ማዕከላት ከኢኮኖሚ ፋይዳቸው በተጨማሪ፣ ለአካባቢው ነዋሪ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር አዲስ አበባ ከጎረቤት ክልሎች ጋር ያላትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር አጠናክረዋል፡፡
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.