በአዲስ አበባ ከተማ ለሚከናወኑ ሁነቶች እንደአስፈላጊነቱ ዕውቅናና የይለፍ ማረጋገጫ እንደሚሰጥ ይታወቃል።
የማንኛውም ሁነት ፈቃድ አሰጣጥና የቁስ የይለፍ ፈቃድ ራሱን የቻለ አሰራር ያለው በመሆኑ ፈቃድ ሰጩ ተቋም በራሱ የደብዳቤ መመሪያና ሎጎ በያዘ መልኩ የሚወጣ ነው።
የከተማ አስተዳደሩም ሆነ የሁነት አመቻችና ፈቃድ ሰጭ ቢሮዎች ሁነት ለማዘጋጀት የጠየቀው አካል አሰራርን በጠበቀ መልኩ ባሳወቀው መሰረት የሁነት ማዘጋጀት የሚችልበት ፈቃድና የመኪናና መሰል ጉዳዮች የይለፍ ማረጋገጫ በሁነት ፈቃጁ ተቋም ደብዳቤ የተቋሙ ሎጎ ባለበት ይሰጠዋል።
ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ የሚገኝ አንድ ፅሁፍ የከተማ አስተዳደሩ በሁለት ሎጎ አንድ ደብዳቤ የይለፍ ማረጋገጫ እንደተሰጠ በማስመሰል
የስም ማጥፋትና የመንግስት ተቋማት አሰራርን እንደማይጠብቁና ህዝብ በመንግስት ላይ እምነት እንዳይኖረው ሆን ተብሎ የማጭበርበር ስራ የሚመስል ይዘት እንዳለው ያመላክታል።
ነገር ግን ይህ መረጃ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን እየገለፅን ማህበረሰቡ እንደዚህ አይነት የተሳሳቱና ዕውነታን ከሚያዛቡ መረጃዎች እራሱን እንዲጠብቅ እያልን እንደዚህና መሰል ጉዳዮች ሲያጋጥም በማንኛውም ጊዜ ለቢሯችን ጥቆማ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ለከተማችን ዘላቂ ሰላምና ለህዝቦቿ በሰላም ወጥቶ መግባት በትጋት እንሰራለን!!
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.