ከንቲባ አዳነች አቤቤ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ከንቲባ አዳነች አቤቤ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ አራዳ ፓርክን ለመጪ ወራት በነፃ እንዲጎበኙ ጋበዙ!

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "ይህ ለከተማችን አዲስ ገፅታን የፈጠረው የውቧ አራዳ ፓርክ ለመላው የከተማችን ነዋሪዎች ለአንድ ወር በነፃ እንድትጎበኙ ክፍት የተደረገ በመሆኑ መጥታችሁ ከግብይት ማዕከላቱ እንድትሸምቱ እንዲሁም በመዝናኛ ማዕከላቱ እንድትዝናኑ ተጋብዛችኋል" ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። 

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ በአራዳ ፓርክ ውስጥ የታሪክ መመልከቻ ጋላሪ፣ ከሱፐር ማርኬት እስከ ባንኮች ያሉ የንግድ ቦታዎች፣ ካፌዎች፣ አዳራሾች፣ ሆቴሎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ጅምናዚየሞች፣ የሳይክልና የመሮጫ ትራኮች እንዲሁም ፋውንቴይንና የልጆች መጫወቻዎች ከበቂ የመኪና ማቆሚያ ጋር ተሟልተው ተዘጋጅተዋል።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.