የአራዳ ፓርክን ይጎብኙ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ አራዳ ፓርክን ለሚቀጥሉት ጥቂት ወራት በነፃ እንዲጎበኝ መግለፃቸው ይታወሳል። በዚህ መሰረት በፓርኩ ለመዝናናትና አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ እንግዶች ሊያውቋቸው የሚገቡ እውነቶች እንደሚከተለው ቀርቧል።
👉ፓርኩ አገልግሎት የሚሰጠው ከጧቱ 12:00 - 5:30 እና ከሰዓት 8:00 - ምሽት 4:00 ሰዓት ይሆናል።
👉ወደ ፓርኩ ለመግባትና ከፓርኩ ለመውጣት መጠቀም ያለብን አራት በሮች 1ኛ. በሲኒማ አምፒር በኩል 2ኛ. በጣይቱ መውጫ በኩል 3ኛ. በቀይ ባህር በኩል እና 4ኛ. በራስ መኮንን ድልድይ በኩል ይሆናል፣
👉ተሽከርካሪ ይዘው ለሚመጡ ጎብኚዎችና አገልግሎት ተጠቃሚዎች መኪና ማቆም የሚቻለው በአራዳ ፓርክ እና ችሎት የመኪና ማቆሚያዎችን (ፓርኪንግ) የሚጠቀሙበት ተዘጋጅቶላቿል ::
👉በፓርኩ ውስጥ የለሙ ሳሮችን ስንጠቀም የጋራ ሃብታችን ስለሆነ እየጠበቅን በሃላፊነት እንድንጠብቅም ጥሪ እናቀርባለን።
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.