የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ!
በተለያዩ የልማት ስራዎች ፈር ቀዳጅ የሆነችው አዲስ አበባ፣ ከ7ኛው ሀገራዊ መርጫ ማግስት በተለያዩ የልማት ስራዎች መገለጥዋን ቀጥላለች፡፡
የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አለመሆናቸውን የተረዳው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ከዚህ ቀደም በእንግልት እና በኃላ ቀር አሰራር ህዝብ ሲማረርባቸው የነበሩ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ይስተዋል የነበረውን ችግር በማስቀረት፣ በአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ቀልጣፋና የተቀናጀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዘመናዊ ተቋማት እየተገነቡ ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
ከዚህም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዘንድ ለዓመታት የቆየውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ታላቅ ስራ ሲሆን፤ በተለይም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ መሆኑ ነዋሪዎች ከተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተቀናጅና በተናበበ እንዲሁም በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲያገኙ አድርጓል።
ቀደም ሲል ቀናትና ሳምንታት ይወስዱ የነበሩ ጉዳዮች፥ ዛሬ በመሶብ የአንድ ማዕከል በደቂቃዎች ውስጥ እልባት ማግኘት ችለዋል፡፡ ከሁሉም በላይ አገልግሎቱ ወደ ነዋሪዎች መቅረቡ ነዋሪዎች ረጅም ርቀት ሳይጓዙ ባሉበት ቦታ በተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል።
እነዚህ ማዕከላት በውስጣቸው ከንግድ ፈቃድ ምዝገባ ጀምሮ እስከ መታወቂያና የውልና ማስረጃ አገልግሎቶች ድረስ እጅግ በርካታ ፋይዳ ያላቸውን ዘርፎች አካትተዋል። በተለይም ለአገልግሎት ፈላጊዎች ምቹ የሆኑ የጥበቃ ስፍራዎች፣ ዲጂታል የሰልፍ መቆጣጠሪያዎች፣ የህፃና ማቆያና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ የሆኑ መሰረት ልማቶችን በመያዛቸው ተገልጋዩ የጊዜ ብክነት እና እንግልት እንዳይገጥመው ታድገዋል፡፡
በአዲስ አበባ የተጀመረውና በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ የሆነው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቁጥሩን ወደ ስምንት ከፍ በማድረግ እንዲሁም በተንቀሳቃሽ አውቶብስ አገልግሎቱን በማስፉት ነዋሪው እፎይታን እንዲያገኘ ማድረግ ተቸሏል።
የልማት ስራዎች የአንድ ወቅት ብቻ አይደሉም፥ ዘመን ተሻጋሪ እንጂ፥ ይቀጥላል!
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.