የ5.7 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው እና ሰፋፊ የህዝብ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የ5.7 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው እና ሰፋፊ የህዝብ የጋራ መገልገያ ስፍራዎችን ለነዋሪው እነሆ ያልንበት ከመገናኛ - ሲኤምሲ አደባባይ ኮሪደርን ዛሬ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በተገኙበት ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል::

ህዝቡ በከፍተኛ ሁኔታ በተሰሩት የመሰረተ ልማት ስራዎች ሲገለገልበት እና ሲዝናናበት እንዲሁም በየኔነት መንፈስ ሲንከባከበው በማየታችን ደስ ብሎናል:: 

ጀመርን እንጂ አልጨረስንም ፣ አዲስ አበባን ቃል በገባነው መሰረት በተሟላ መልኩ እንደ ስሟ ውብ አበባ እንድትሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን ቀሪ የኮሪደር ስራችንን እያሰፋን እንሄዳለን::

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.