የተከታታይ የምስል አቅርቦቱን ምንጀምረው በአዲስ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የተከታታይ የምስል አቅርቦቱን ምንጀምረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው። በሁለተኛው ምዕራፍ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ምን እየተከናወነ ነው?

👉ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ በአዲስ አበባ በ8 አካባቢዎች እየተከናወነ ነው።

👉በሁለተኛው ምዕራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት በአጠቃላይ 2 ሺህ 879 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፤ 240 ኪሎ ሜትር የአስፋልት እንዲሁም 237 ኪሎሜትር እግረኛ መንገድ በመገንባት ላይ ነው።

👉በስምንቱም የኮሪደር ልማት ስፍራዎች 32 የህጻናት መጫዎቻ ፤79 የሚሆኑ ህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም 114 የመኪና ማቆሚያ ፓርኪንግና የታክሲና አውቶብስ ተርሚናሎችን ያካተተ መሰረተ ልማት ይከናወናል።

👉ከትራንስፖርት መሰረተ ልማቶች መካከል 58 በሚሆኑ አካባቢዎች ላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ጣቢያዎች ይኖራሉ።

👉ከ100 ኪሎሜትር በላይ የሚሆን የብስክሌት መንገድም በመገንባት ላይ ነው።

👉የከተማዋ ነዋሪዎች ጤናቸውን የሚጠብቁባቸው 17 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋሉ።

👉በኮሪደር ልማት ስራው ከእንጦጦ -ቀበና-ግንፍሌ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ-ወዳጅነት-ፒኮክ የሚደርሱ ሁለት የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችም እየተከናወኑ ነው።

#PMOEthiopia


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.